ሰላምታዬ ለሁሉ ለኢትዮጵያውያን ፤ ለወዳጆች እና ለቤተሰቦች ይድረስ

ደግ 27 ታህሳስ 27 ቀን 2011 በሴኔጋል ድርጅታችን ፍቃድ ካገኘ በኃላ በኬፕ ቨርዴ ለ 7 ተከታታይ አመታት የማህበረሰብ ስራ ሲሰራ ቆይተ በኋላ በዚያው አመት በ2021 ወደ እናት ሀገራችን ኢትዮጵያ ተዘዋውሯል። ደግ በወሎፍ (ሴኔጋል) ቋንቋ ሲሆን ትርጉሙም እውነት ማለት ነው፤በአማርኛ ቋንቋ ደግሞ ደግነትም ማለት ነው። 12 ዓመታት የማህበረሰብ እና የእርዳታ ስራን በመስራት ፣ እንዲሁም ይህ ሁሉ ጊዜ የሶሺዮሎጂካል ወይም ማህብረሰብ በራዕዩ የተደገፈ ዕውቀትለአፍሪካ ማለትም የኢትዮ-ፓን አፍሪካ ማእከል ፣ (ሲኢፒ) ለአፍሪካ አንድነት እና ለሰላም የፓን አፍሪካን ዩኒቨርሲቲ ለመስራት ፍላጎት አሳድሮብናል። ይህንን ግብ ለማሳካት ፓን አፈሪካኒዚም ለማሳካት ያሰብናቸው ስራዎች አሉ የወጣቶች ሙዚቃ ባንድ፣ የስኮላርሺፕ ፕሮዳክሽን ድርጅት ማለትም ማህበረሰቡ ጋር መልዕክት ለማድረስ ማህበረሳባዊ ድርጅት ይማል። ማዕከሉ ቀድሞውንም ሙሉ በሙሉ የታጠቀ እና ሁለገብ ነው፡ የተለያዩ የአፍሪካ እና የውጭ ቋንቋዎች፣ግብርና፣ ቪዥዋል ጥበባት፣ ቴክኒሻኖች በጋራ ለመስራት የተሰማሩ፡ አርክቴክቶች፣ ሶሺዮሎጂስቶች፣ ሳይኮሎጂስቶች፣ መልቲሚዲያ፣ ሙዚቃ ወዘተ. ማሳያችን ደግሞ አሁን 5 የማህበራዊ ድርጅቶችን በጋራ እንድንመራ እውቅና ተሰጥቶናል በሚከተሉት ዘርፎች 1. ማህበረሰብ 2. ትምህርት 3. አካባቢ 4. ስነ ጥበብ እና 5. ሙዚቃ እና ደግሞ በአንድነት የስነ ህንጻ ዝግጅት ትምህርት ለመስጠት ። በአዲስ አበባ ውስጥ CEP ዲዛይን ፣ በሚቀጥለውም ዓመት መጀመሪያ ላይ ለግንባታው ሲባል የህዝብ መሬት ለመጠየቅ ሀሳብ አቅርቧል ። ከእናንተ የምንጠብቀው ወሳኝ ጉዳይ፡- በነዚህ 4 ዓመታት ውስጥ ወደ 50 የሚጠጉ ሰዎች ጋር አብረን እየሰራን እንገኛለን፤ ለቀጣይነት ለመዘጋጀት ከመሥራቾቹ ጋር እንዲሁም ከቤተሰቤ ጋር በሙሉ ድጋፍ ጋር ከሞላ ጎደል ስንሰራ ቆይተናል ። ስራው አገር ብሎም አሃጉር አቀፋዊ እንዲሆን እንደ ኬፕ ቨርዴ፣ ሴኔጋል፣ ደቡብ ሱዳን፣ ፈረንሳይ እና አሜሪካ ያሉ ሀገራት ጋር ጥሩ ግንኙነቶች ፈጥረናል። ስለዚህ፣ 3ቱ ዋና ዋና እርዳታ ከእናንተ በትህትና የምንጠበቀው ። 1. የቤት ኪራይ ክፍያ; 2. ለበጎ ፈቃደኞች ምግብ; 3. ለአምራቾች፣ ለአሰልጣኞች እና ለበጎ ፈቃደኞች ለእነሱ የሚሆን ትንሽ ድጎማ ; በዚህ ድጋፍ ለብዙ ሰዎች የደስታን በሮች እንድንከፍት የእርዳታ ቁልፎችን እንደምትሰጡን ሙሉ በሙሉ እናምናለን, ህፃናት እና ወጣቶች, የስደተኛ ቤተሰቦች እና ከጦርነት እልቂት የተረፉ ሰዎች እርዳታ እየሰጠን እንገኛለን ምክንያቱም እኛ ሥራ ለመፍጠር, የስልጠና እድሎችን እና ተሰጥኦዎችን ለማፍራት ነው የምንሰራው እና ኃይል ለማውጣት ከመሀል አዲስ አበባ ለመላው አፍሪካ። በዚህ የሰላም አፍሪካ ፕሮጀክት ሰላምን፣ ፍቅርን፣ አንድነትን፣ እውነትን፣ ራስን መምራትን፣ ኃላፊነትን፣ ተግባርን እና ሉዓላዊነትን፣ ይህንን የሚያበረታቱ እና የሚመሩ ዋና ዋና እሴቶችን መጠቀም ፤ አፍሪካም በልጆችዋ ትታደስ፡፡. ጊዜው አሁን ነው. ኢትዮጵያ ለአፍሪካ አንድነት ከዜጎቿ ጀምሮ በሞራል ተጠያቂ የሆነች ሀገር ነች፤ አሁን እያደረግን ያለነው። ይህ ለኢትዮጵያም ለአፍሪካ ትልቅ ጉዳይ ነው። ከኛ ጋር በተመሳሳይ መንገድ በጉዞአችን እንደምትሄድ ተስፋ እናደርጋለን። ሁላችሁንም እናመሰግናለን! እግዚአብሔር ይርዳን።

Post a Comment

Previous Post Next Post